Wednesday, March 1, 2023

የ6ወር የቢ ኤስ ሲ እቅድ አፈጻጸም ምዘና

 

ቀን 22/6/2015 .

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የእቅድ በጀት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት በትምህርት ተቋማት ሲያካሂድ የቆየውን 2015 . 6ወር የቢ ኤስ እቅድ አፈጻጸም ምዘና በዛሬው እለት አጠናቀቀ፡፡

 

ምዘናው በሁሉም የመንግስት አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ጨምሮ በክፍለከተማ እና ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤቶች አስሩን ዋና ዋና ግቦች መነሻ በማድረግ የተካሄደ ሲሆን ቀደም ሲል ምዘናውን ለሚያካሂዱ 400 በላይ ለሚሆኑ መዛኞችና አስተባባሪዎች ኦረንቴሽን መሰጠቱን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የእቅድ በጀት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ አቶ ጌታሁን ለማ ገልጸዋል፡፡ 

 

በትምህርት ተቋማት የሚካሄደው የቢ ኤስ እቅድ አፈጻጸም ምዘና ተቋማቱ ያሉበትን ሁኔታ በማወቅ ደረጃቸውን እንዲያሻሽሉ ከማስቻሉ ባሻገር በተቋማቱ መካከል የውድድር መንፈስ በመፍጠር በቀጣይ የተሻለ ስራ መስራት  እንዲችሉ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ዳይሬክተሩ ጠቁመው ምዘናው ያለምንም እንከን እንዲካሄድ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ለተወጡ መዛኞችና ተመዛኝ  ተቋማት ምስጋና አቅርበዋል፡፡

 

 

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

 

 Blog: - https://aacaebc.blogspot.com

 

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...

 

TikTok- tiktok.com/@aaeducationbureau

 

Telegram https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

 

Twitter https://twitter.com/aacaebc

 

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

 

Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/

No comments:

Post a Comment