Thursday, February 23, 2023

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ቀደም ሲል ሴክተሩን በአመራርነት አገልግለው ወደ ሌላ ዘርፍ ለሄዱ አመራሮች የሽኝት መርሀ ግብር አካሄደ፡፡

 

ቀን 16/6/2015 .

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ቀደም ሲል ሴክተሩን በአመራርነት አገልግለው ወደ ሌላ ዘርፍ ለሄዱ አመራሮች የሽኝት መርሀ ግብር አካሄደ፡፡

 

ሽኝቱ የተደረገላቸው ቀደም ሲል በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በምክትል ቢሮ ኃላፊነት ሲያገለግሉ ለነበሩት ለአቶ ሳመሶን መለሰ እና አቃቂ ቃሊቲ ክፍለከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ በመሆን ሲያገለግሉ ለቆዩት አቶ አለልኝ ወልዴ ሲሆን በሽኝት መርሀ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የማኔጅመንት እና የፕሮሰስ ካውንስል አባላትን ጨምሮ የክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በሽኝት ፕሮግራሙ ባስተላለፉት መልዕክት በዛሬው እለት የሚሸኙት አመራሮች በትምህርት ሴክተሩ በነበራቸው ቆይታ በሴክተሩ ለተመዘገበው ውጤት ያበረከቱት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው አሁን በተመደቡበት ዘርፍም ለትምህርት ሴከክተሩ የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ እምነታቸው መሆኑን በመግለጽ በተመደቡበት ሴክተር መልካም እድል እንዲገጥማቸውና በስራቸውም ውጤታማ እንዲሆኑ የመልካም ምኞት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

 

ሽኝቱ የተደረገላቸው አቶ ሳምሶን መለሰ እና አቶ አለልኝ ወልዴ በመርሀ ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት በአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ እና በክፍለከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤቶች ለተደረገላቸው የክብር ሽኝት ላቅ ያለ ምስጋና  በማቅረብ በትምህርት ሴክተሩ በነበራቸው ቆይታ ያካበቱት የስራ ልምድም ሆነ በጋራ የመስራት ባህል አሁን በተመደቡበት ሴክተር ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያግዛቸው መሆኑን አስረድተዋል፡፡

 

 

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

 

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...

 

TikTok- tiktok.com/@aaeducationbureau

 

Telegram https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

 

Twitter https://twitter.com/aacaebc

 

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

 

Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/

 

Website: - aaceb.gov.et

 

Email;- aacaebc@gmail.com

 

Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/

No comments:

Post a Comment