Monday, February 27, 2023

የ6 ወር የቢ ኤስ ሲ እቅድ አፈጻጸም ምዘናን በዛሬው ዕለት ማካሄድ ጀመረ

 

ቀን 20/6/2015 .

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የእቅድ በጀት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት 2015 . 6 ወር የቢ ኤስ እቅድ አፈጻጸም ምዘናን በዛሬው ዕለት ማካሄድ ጀመረ፡፡

 

ምዘናው እስከ 2014 . ድረስ በለውጥና መልካም አስተዳደር ዳይሬክቶሬት አማካይነነት ሲካሄድ ቆይቶ ዘንድሮ በእቅድ በጀት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት እንዲመራ በተወሰነው መሰረት ከትምህርት ቤት ጀምሮ እስከ ትምህርት ቢሮ ድረስ አስሩን ዋና ዋና ግቦች መነሻ በማድረግ የሚካሄድ ሲሆን  ቀደም ሲል 400 በላይ ለሚሆኑ መዛኞችና አስተባባሪዎች በምዘናው ሂደትና ለመመዘኛነት በተዘጋጁ መስፈርቶች ዙሪያ ኦረንቴስን መሰጠቱ  ይታወቃል፡፡ 

 

ምዘናው በዛሬው እለት በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተጀመረ መሆኑን እና ከነገ ጀምሮ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ የወረዳና ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤቶች እንደሚመዘኑ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የእቅድ በጀት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ለማ ገልጸው በትምህርት ተቋማት የሚካሄድ የቢ ኤስ እቅድ አፈጻጸም ምዘና ተቋማቱ ያሉበትን ደረጃ ለማወቅ ከማስቻሉ ባሻገር በተቋማቱ መካከል የውድድር መንፈስ በመፍጠር በቀጣይ የተሻለ ስራ ለመስራት  እንደሚያስችል አስታውቀዋል፡፡

 

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

 

 Blog: - https://aacaebc.blogspot.com

 

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...

 

TikTok- tiktok.com/@aaeducationbureau

 

Telegram https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

 

Twitter https://twitter.com/aacaebc

 

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

 

Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/

No comments:

Post a Comment