Wednesday, March 15, 2023

#ማስታወቂያ!

 

ቀን 6/7/2015 .

 

#ማስታወቂያ!

 

በ2014 ዓ.ም በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ሀገራቀፍ ፈተና የላቀ ውጤት አምጥታችሁ የውጪ ሀገር የትምህርት እድል /Scholarship /  ለተሰጣችሁ  ተማሪዎች

 

በ2014 ዓ.ም በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ሀገራቀፍ ፈተና የላቀ ውጤት አምጥታችሁ የውጪ ሀገር የትምህርት እድል/Scholarship / የተሰጣችሁ 273 ተማሪዎች የውጪ ሀገር ትምህርቱ የሚጀመረዉ ከመስከረም 2016 ዓ.ም ጀምሮ በመሆኑ ቀደም ሲል ወደተመደባችሁባቸው ዩኒቨርስቲዎች እንድትገቡ እናሳስባለን፡፡

 

ለውጪ ሀገር ትምህርታችሁ የሚያግዝ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርትና ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ከተመደባችሁባቸው ዩኒቨርስቲዎች ጋር በመነጋገር የሚፈጸም ይሆናል፡፡

 

ማስታወሻ፤- በዚህ ጉዳይ በተናጠል ወደ ትምህርት ሚኒስቴር የሚመጣ ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

 

የትምህርት ሚኒስቴር!

 

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

 

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...

Ticktack- tiktok.com/@aaeducationbureau

Telegram https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: - aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/

Tuesday, March 14, 2023

አለም አቀፉ የሴቶች ቀን በድምቀት ተከበረ ::

ቀን 5/7/2015 .

 

አለም አቀፉ የሴቶች ቀን በድምቀት ተከበረ ::

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አለም አቀፉን የሴቶች ቀን(march 8) እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ በሚል መሪ ቃል አጠቃላይ የቢሮው ሰራተኞች በተገኙበት አከበረ።

 

ቀኑ ዘንድሮ በሀግራችን 47 እንዲሁም በአለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ 112 ጊዜ እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ በሚል መሪ ቃል በመከበር ላይ እንደሚገኝ የቢሮው የስርአተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወይዘሮ አበባ ዘውዴ ገልጸው ቀኑ በሀገራችን መከበር ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ የሴቶች እኩልነት ህገመንግስታዊ ዋስትና እንዲያገኝ ከማስቻሉ ባሻገር በተለያዩ የልማት መስኮች የሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን አስታውቀዋል።

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳኘው ገብሩ በመርሀ ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት ቀኑን ማክበር የሚያስፈልገው ለሴቶች የሚገባቸውን ክብር እና በተለያዩ መስኮች ላበረከቱት አስተዋጽኦ ተገቢውን እውቅና በመስጠት መሆኑን ጠቁመው በትምህርት ዘርፉ የሴቶች ተሳትፎም ሆነ ውጤታማነት ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍተ እድገት እያሳየ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

 

አለም አቀፉ የሴቶች ቀን ተከብሮ የሚውልበት ዋነኛ አላማ በሴቶች ትግል የተገኙ ውጤቶችን በማስቀጠል ለሁለንተናዊ ተጠቃሚነታቸው ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማድረግን ታሳቢ አድርጎ እንደመሆኑ በሁሉም ዘርፍ የሴቶችን ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ የቢሮው ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሲሳይ እንዳለ አስገንዝበዋል።

 

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

 

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...

Ticktack- tiktok.com/@aaeducationbureau

Telegram https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: - aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/

 

በትምህርት ብርሀን ምዘና አተገባበር ዙሪያ ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡

 

ቀን 5/7/2015 .

 

በትምህርት ብርሀን ምዘና አተገባበር ዙሪያ ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርዓተ ትምህርት ዝግጅትና ትግበራ ዳይሬክቶሬት 2015 . የትምህርት ብርሀን ምዘና አተገባበር ዙሪያ ከክፍለከተማና ወረዳ የጎልማሶች ትምህርት ባለሙያዎች ጋር ውይይት አካሄደ፡፡

 

የትምህርት ብርሀን ምዘናው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከዚህ በፊት ለሁለት ዙር መካሄዱን እና በዚህ ሂደትም 17,216 ጎልማሶችና ወጣቶች ምዘናውን ወስደው 13,511 የሚሆኑት 50% እና ከዚያ በላይ ማስመዝገባቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርአተ ትምህርት ዝግጅትና ትግበራ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ታለማ አስታውቀዋል፡፡

 

ዳይሬክተሩ አክለውም የዘንድሮው የትምህርት ብርሀን ምዘና ከመጋቢት 11/2015 . ጀምሮ እስከ መጋቢት 30/2015. ድረስ በሁሉም የጎልማሶች ትምህርት መስጫ ጣቢያዎች እንደሚሰጥ ጠቁመው ዘንድሮ 17,000 የሚሆኑ ጎልማሶችና ወጣቶችን 50% ከዛ በላይ እንዲያመጡ ለማስቻል ቢሮው ግብ ማስቀመጡንም አስገንዝበዋል፡፡

 

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የጎልማሶች ትምህርት ባለሙያው አቶ ልኡል መርጋ በበኩላቸው 2015. የትምህርት ብርሀን ምዘና ሂደቱ ስኬታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ተግባር እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸው ምዘናው የማንበብ መጻፍና ማስላት ክህሎቶችን መሰረት አድርጎ እንደሚሰጥ እና 50% እና ከዚያ በላይ የሚያስመዘግቡ ተመዛኞች በመደበኛው ትምህርት 2 ክፍል ካጠናቀቁ ተማሪዎች ጋር አቻ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት እንደሚሰጣቸው አስታውቀዋል፡፡

 

ምዘና ወስደው የሚፈለገውን ማለፊያ ውጤት የሚያስመዘግቡ ተመዛኞች በመደበኛ ትምህርት 3 ክፍል ገብተው መማር የሚችሉበት እድል መመቻቸቱን እና በምዘናው 50% በታች የሚያስመዘግቡ ጎልማሶችና ወጣቶች በድጋሜ እንደሚመዘኑ አቶ ልኡል አስረድተዋል፡፡

 

 

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

 

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...

Ticktack- tiktok.com/@aaeducationbureau

Telegram https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: - aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምራል፡፡

 

ቀን 5/7/2015 .

 

አዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 2 ዓመት የስራ ዘመን 3 መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምራል፡፡

 

ምክርቤቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 2015 ዓም የመጀመሪያ 6 ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት  ላይ ይወያያል፣ ረቂቅ  ማሻሻያ አዋጅ ላይ  ተወያይቶ ማጽደቅና  ሌሎች አጀንዳዎች ላይ እንደሚወያይ ይጠበቃል።

 

ከንቲባ አዳነች አቤቤ  የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2015 ዓም የመጀመሪያ 6 ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት  ያቀረቡ ሲሆን በሪፖርታቸዉ ፡- የፀረ-ሌብነት ትግልን በማጠናከር፡ የህግ በላይነት የማስከበር፣ የተጠያቂነት ለማስፈን በሕዝባዊ ንቅናቄ የተደገፉ ስራ እየተሰራ ነው፡፡ የፀረ-ሙስና እና ስነ- ምግባር ኮሚሽን በአዲስ መልክ ተደራጅቶ ስራ ጀምሮአል:: በከተማ ደረጃ የፀረ ሙስና ንቅናቄ ግብረ ሃይል ተቋቁሞ ከህብረተሰቡ ጥቆማ በመቀበል  215 አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ደላሎች በህግ ቁጥጥር ስር ሆነው ጉዳያቸው በፍትህ ሂደት ላይ ይገኛል፡፡

ይሄም በዝርዝር ሲታይ የካ /ከተማ 40 ንፋስ ስልክ ላፍቶ 42  ለሚ ኩራ 48 ልደታ 26 አቃቂ ቃሊቲ 33 በማዕከልና ሴክተሮች 26 የሚሆኑ በህግ ተጠያቂ ሆነዋል፡፡

 

በተጨማሪም ከማዕከል አስከ ወረዳ ባሉ ተቋማት 3,584 አመራርና ሰራተኞች በተለያዩ የዲሲፕሊን ግድፈቶች አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ተደርጓል ያሉ ሲሆን፡፡

 

ባለፉት 6 ወራት የህብረተሰቡን የኑሮ ጫና ለማቅለል የተከናወኑ ዋና ዋና ስራዎችን በተመለከተ :-

 

  የምርት አቅርቦትን በማሳደግ የዋጋ ግሽበትና የኑሮ ዉድነትን ለማረጋጋት በተሰራው ስራ፤ 170,128 የሰብል ምርት በገበያ ማዕከላት ትስስር መፍጠር ተችሏል፡፡

 

  የእሁድ ገበያ(Sunday Market) በሁሉም /ከተሞች 137 የገበያ መዳረሻዎች በማስፋፋት የግብርና ምርቶች ከአርሶ አደሩ ወደ ተጠቃሚው በቀጥታ እንዲደርሱ በማድረግ ሸማቹ በተመጣጣኝ ዋጋ ምርቶችን እንዲያገኝ እየተደረገ ይገኛል

 

  የመሠረታዊ ፍጆታ ሸቀጦች አቅርቦት ለህብረትሰቡ በፍትሃዊነት ተደራሽ ከማድረግ አንፃር 272,777 ስኳር ማሰራጨት ተችሏል።

 

  10.9  ሚሊዮን ሊትር ፓልም ዘይት ማሰራጨት ተችሏል

 

  194 ሚሊዮን የሸገር ዳቦ በሸገር ዳቦ በመሽጫ ሱቆች ማሰራጨት ተችሏል

 

  ከሸገር የዳቦ ፋብሪካ በተጨማሪ የተገነቡት የዳቦ ፋብሪካዎች ቁጥር 25 ማድረስ ተችሏል

 

  የከተማ አስተዳደሩ በመደበው 1.4 ቢሊዮን የተዘዋዋሪ ብድር በመጠቀም በድምሩ 356,761 ኩንታል ጤፍ በሸማች ኅብረት ሥራ ማህበራት በኩል በማቅረብ ገበያ የማረጋጋት ስራ ተሰርቷል

 

  ለትምህርት ቤት ምገባ የወቅቱን ኑሮ ውድነት መነሻ በማድረግ በዓመት ተጨማሪ 54 ሚሊዮን ብር ተመድቦ የመጋቢ እናቶችን ጫና የመቀነስ እና የተማሪዎችን ምገባ የተሻለ ለማድረግ የሚያስችል ስራ ተሰርቷል

 

  በዘላቂነት የኑሮ ውድነት ጫና  ለመቀነስና ገበያን ለማረጋጋት በአዲስ አበባ የመግቢያ በሮች ማለትም በኮልፌ በንፋስልክ ላፍቶ በለሚ ኩራ እና በአቃቂ ክፍለ ከተሞች አራት ትላልቅ ሁለገብ የግብርና ምርቶች ማከፋፈያ ማዕከላት ግንባታ በዚህ በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ 24 ሰዓታት እየተሰራ ይገኛል

 

. የሌማት ትሩፋት ስራችን አዲስ የልማት ከፍታ ጉዞ በሚል ከጥቅምት 27 ጀምሮ 52,228 ለሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ስልጠና በመስጠት ወደ ተግባር እንዲገቡ ተደርጓል፡፡ በተለይ የወተት፣ የዶሮ ስጋ እንቁላል እና የማር ምርታማነት በማሳደግ እንዲሁም የጓሮ አትክልት በማምረት ያለንን አቅም እና ጸጋ ወደ ተግባር በመቀየር የከተማችንን ነዋሪዎች የኑሮ ጫና ለማቅለል እየተሰራ ይገኛል

 

. በከተማችን በቀን አንድ ግዜ መመገብ ለማይችሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ላሉ ነዋሪዎች 15 የምገባ ማዕከላት 30ሺህ ለሚሆኑ ነዋሪዎች የምገባ ፕሮግራም ተጠቃሚ ማድረግ ተችላል ብለዋል::

 

 

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

 

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...

Ticktack- tiktok.com/@aaeducationbureau

Telegram https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: - aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/