Friday, March 3, 2023

በተሻሻለው የስርዓተ ጾታ መመሪያ እና ተዛማጅ ጉዳዮች

 

ቀን 24/6/2015 .

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርዓተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ዳይሬክቶሬት በተሻሻለው የስርዓተ ጾታ መመሪያ እና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ የአሰልጣኞች ስልጠና በመስጠት ላይ መሆኑን አሳወቀ።

 

በስልጠናው የክፍለ ከተማ የዘርፈ ብዙ ባለሙያዎችና ሱፐርቫይዘሮችን ጨምሮ ከተመረጡ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ የስነ ዜጋና ስነምግባር መምህራን እና የጋይዳንስና ካውንስሊንግ ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።

 

በስልጠናው መክፈቻ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርአተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወይዘሮ አበባ ዘውዴ እንዳስታወቁት የስርዓተ ጾታ መመሪያው 2007 . በኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስተር ተዘጋጅቶ በየትምህርት ተቋማቱ ተግባራዊ ሲደረግ መቆየቱን ጠቁመው መመሪያው ዳግም በአዲስ መልክ ወቅታዊ ሁኔታዎችን ታሳቢ አድርጎ በመዘጋጀቱ በዚህ የአሰልጣ ኞች ስልጠና ተሳታፊ የሆኑ መምህራንም ሆኑ የትምህርት ባለሙያዎች በየትምህርት ቤቶቻቸው መመሪያውን መሰረት በማድረግ ለትምህርት ማህበረሰቡ ተገቢውን ግንዛቤ መፍጠር እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።

 

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርአተ ጾታ ማስረጽና ማካተት ባለሙያ አቶ ደረጀ ደምሴ በመርሀ ግብሩ ጾታዊ ጥቃትንም ሆነ በህጻናት ላይ የሚደርሱ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን ለመከላከል የወጡ አለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ የህግ ማእቀፎችን መሰረት በማድረግ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና የሰጡ ሲሆን ሰልጣኞቹም በቀረቡ የመወያያ ሀሳቦች ዙሪያ በቡድንና በጋራ ውይይት አድርገዋል።

 

 

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

 

 Blog: - https://aacaebc.blogspot.com

 

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...

 

TikTok- tiktok.com/@aaeducationbureau

 

Telegram https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

 

Twitter https://twitter.com/aacaebc

 

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

 

Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/

Wednesday, March 1, 2023

ማስታወቂያ!

 

ቀን 22/6/2015 .

 

የተማሪዎች ምገባ ክትትልና ቁጥጥር ባለሙያ መደብ ላይ ተወዳድራችሁ ያለፋችሁ ተወዳዳሪዎች ስማችሁን ከታች ባለው ሊንክ ላይ መመልከት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ከእሮብ ማለትም ከ29/6/2015 ዓ.ም ጀምሮ በየተመደባችሁበት ክፍለ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ፅ/ቤት በአካል በመሄድ ምደባችሁን እንድትወስዱ እናሳውቃለን፡፡

 

https://aacaebc.wordpress.com/2023/03/01/ቀን-22-6-2015-ዓ-ም/

 

 

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

 

 Blog: - https://aacaebc.blogspot.com

 

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...

 

TikTok- tiktok.com/@aaeducationbureau

 

Telegram https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

 

Twitter https://twitter.com/aacaebc

 

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

 

Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/

የ6ወር የቢ ኤስ ሲ እቅድ አፈጻጸም ምዘና

 

ቀን 22/6/2015 .

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የእቅድ በጀት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት በትምህርት ተቋማት ሲያካሂድ የቆየውን 2015 . 6ወር የቢ ኤስ እቅድ አፈጻጸም ምዘና በዛሬው እለት አጠናቀቀ፡፡

 

ምዘናው በሁሉም የመንግስት አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ጨምሮ በክፍለከተማ እና ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤቶች አስሩን ዋና ዋና ግቦች መነሻ በማድረግ የተካሄደ ሲሆን ቀደም ሲል ምዘናውን ለሚያካሂዱ 400 በላይ ለሚሆኑ መዛኞችና አስተባባሪዎች ኦረንቴሽን መሰጠቱን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የእቅድ በጀት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ አቶ ጌታሁን ለማ ገልጸዋል፡፡ 

 

በትምህርት ተቋማት የሚካሄደው የቢ ኤስ እቅድ አፈጻጸም ምዘና ተቋማቱ ያሉበትን ሁኔታ በማወቅ ደረጃቸውን እንዲያሻሽሉ ከማስቻሉ ባሻገር በተቋማቱ መካከል የውድድር መንፈስ በመፍጠር በቀጣይ የተሻለ ስራ መስራት  እንዲችሉ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ዳይሬክተሩ ጠቁመው ምዘናው ያለምንም እንከን እንዲካሄድ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ለተወጡ መዛኞችና ተመዛኝ  ተቋማት ምስጋና አቅርበዋል፡፡

 

 

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

 

 Blog: - https://aacaebc.blogspot.com

 

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...

 

TikTok- tiktok.com/@aaeducationbureau

 

Telegram https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

 

Twitter https://twitter.com/aacaebc

 

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

 

Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/

ለተማሪዎቻችን ምግብ ብቻ ሳይሆን ፍቅርንም እየሰጠን ሃገሩን የሚወድ ጠንካራ ዜጋ የማፍራት ስራችንን እንቀጥላለን፡-ከንቲባ አዳነች አቤቤ

 

ቀን 22/6/2015 .

 

ለተማሪዎቻችን ምግብ ብቻ ሳይሆን ፍቅርንም እየሰጠን ሃገሩን የሚወድ ጠንካራ ዜጋ የማፍራት ስራችንን እንቀጥላለን፡-ከንቲባ አዳነች አቤቤ

 

8ኛው የአፍሪካ የትምህርት ምገባ ቀንን የተለያዩ የአፍሪካ ሃገራት የትምህርት ሚኒስትሮች የዓለም የምግብ ፕሮግራም ኃላፊዎች የተባበሩት መንግስታት የምግብ እና የትምህርት ኮሚሽነሮች እንዲሁም የተለያዩ ሃገራት የምገባ ኤጀንሲዎች በተገኙበት በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ መከበሩን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ / አዳነች አቤቤ አስታውቀዋል::

 

ከንቲባ አዳነች በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ትላንት ስንጀምረው ቀላል ይመስል የነበረው የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራም ዛሬ ላይ አድጎ እና አለምአቀፍ እውቅናን አግኝቶ የተለያዩ ሃገራት ልምድ የሚወስዱበት ስራ በመሆኑ እጅግ ደስ ይለናል ብለዋል::

 

አሁንም ትውልድ የመገንባት ስራችን በማጠናከር "ለተማሪዎቻችን ምግብ ብቻ ሳይሆን ፍቅርንም እየሰጠን ሃገሩን የሚወድ ጠንካራ ዜጋ የማፍራት ስራችንን እንቀጥላለን "ሲሉም አስታውቀዋል::

 

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

 

 Blog: - https://aacaebc.blogspot.com

 

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...

 

TikTok- tiktok.com/@aaeducationbureau

 

Telegram https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

 

Twitter https://twitter.com/aacaebc

 

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

 

Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/

የኬጂ ተማሪዎች የአዲስ ዙ ፓርክ ትምህርታዊ ጉብኝት

 

ቀን 22/6/2015 .

 

በልደታ ክፍለ ከተማ የካራማራ ቅድመ መጀመሪያ እና የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት የኬጂ ተማሪዎች የአዲስ    ፓርክ ትምህርታዊ ጉብኝት፡፡

 

በልደታ ክፍለ ከተማ በሚገኘው የካራማራ ቅድመ መጀመሪያ እና የመጀመሪያ ደረጃ /ቤት ውስጥ በመማር ላይ የሚገኙ የኬጂ ተማሪዎች በትምህርት ቤቱ የሀገርህን እወቅና የአካባቢ ጥበቃ ክበብ አማካኝነት በአዲስ    ፓርክ  ትምህርታዊ ጉብኝት አድርገዋል፡፡

 

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

 

 Blog: - https://aacaebc.blogspot.com

 

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...

 

TikTok- tiktok.com/@aaeducationbureau

 

Telegram https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

 

Twitter https://twitter.com/aacaebc

 

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

 

Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/