Monday, February 27, 2023

የ6 ወር የቢ ኤስ ሲ እቅድ አፈጻጸም ምዘናን በዛሬው ዕለት ማካሄድ ጀመረ

 

ቀን 20/6/2015 .

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የእቅድ በጀት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት 2015 . 6 ወር የቢ ኤስ እቅድ አፈጻጸም ምዘናን በዛሬው ዕለት ማካሄድ ጀመረ፡፡

 

ምዘናው እስከ 2014 . ድረስ በለውጥና መልካም አስተዳደር ዳይሬክቶሬት አማካይነነት ሲካሄድ ቆይቶ ዘንድሮ በእቅድ በጀት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት እንዲመራ በተወሰነው መሰረት ከትምህርት ቤት ጀምሮ እስከ ትምህርት ቢሮ ድረስ አስሩን ዋና ዋና ግቦች መነሻ በማድረግ የሚካሄድ ሲሆን  ቀደም ሲል 400 በላይ ለሚሆኑ መዛኞችና አስተባባሪዎች በምዘናው ሂደትና ለመመዘኛነት በተዘጋጁ መስፈርቶች ዙሪያ ኦረንቴስን መሰጠቱ  ይታወቃል፡፡ 

 

ምዘናው በዛሬው እለት በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተጀመረ መሆኑን እና ከነገ ጀምሮ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ የወረዳና ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤቶች እንደሚመዘኑ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የእቅድ በጀት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ለማ ገልጸው በትምህርት ተቋማት የሚካሄድ የቢ ኤስ እቅድ አፈጻጸም ምዘና ተቋማቱ ያሉበትን ደረጃ ለማወቅ ከማስቻሉ ባሻገር በተቋማቱ መካከል የውድድር መንፈስ በመፍጠር በቀጣይ የተሻለ ስራ ለመስራት  እንደሚያስችል አስታውቀዋል፡፡

 

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

 

 Blog: - https://aacaebc.blogspot.com

 

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...

 

TikTok- tiktok.com/@aaeducationbureau

 

Telegram https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

 

Twitter https://twitter.com/aacaebc

 

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

 

Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/

Further on Congruency and similarity 4

Friday, February 24, 2023

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ!

 

ቀን 17/6/2015 .

 

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ!

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በተማሪዎች ምገባ አገልግሎት ቁጥጥር እና ክትትል ባለሙያነት ተመዝግባችሁ ለፅሑፍ ፈተና የተመረጣችሁ ከታች ባለው ሊንክ ስም ዝርዝር ውስጥ የተካተታችሁ ቅዳሜ 18/06/2015 ዓ/ም ከጥዋቱ 3፡00 የፅሑፍ ፈተና ስለሚሰጥ ማንነታችሁን የሚገልፅ መታወቂያ በመያዝ  በዳግማዊ ምኒሊክ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተገኝታችሁ ፈተና እንድትወስዱ እናሳውቃለን፡፡

 

https://aacaebc.wordpress.com/2023/02/24/የፈተና-ጥሪ-ማስታወቂያ/

 

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

 

 Blog: - https://aacaebc.blogspot.com

 

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...

 

TikTok- tiktok.com/@aaeducationbureau

 

Telegram https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

 

Twitter https://twitter.com/aacaebc

 

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

 

Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/


Thursday, February 23, 2023

ትምህርት በሬዲዮ

 

ቀን 17/6/2015 .

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በ2015 የትምህርት ዘመን በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሰረት ያዘጋጃቸውን የትምህርት በሬዲዮኖች በከተማ አስተዳደሩ የሚገኙ ሁሉም የግል ፣ የመንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከቢሮ የቴሌግራም ገጽ

https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

ላይ በመውስድ ለመማር ማስተማር ስራው እገዛ እንዲያደርግ እና ለተማሪዎች ተደራሽ እንዲሆን እንድታደርጉ እናሳውቃለን፡፡

 

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

 

 Blog: - https://aacaebc.blogspot.com

 

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...

 

TikTok- tiktok.com/@aaeducationbureau

 

Telegram https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

 

Twitter https://twitter.com/aacaebc

 

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

 

Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ቀደም ሲል ሴክተሩን በአመራርነት አገልግለው ወደ ሌላ ዘርፍ ለሄዱ አመራሮች የሽኝት መርሀ ግብር አካሄደ፡፡

 

ቀን 16/6/2015 .

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ቀደም ሲል ሴክተሩን በአመራርነት አገልግለው ወደ ሌላ ዘርፍ ለሄዱ አመራሮች የሽኝት መርሀ ግብር አካሄደ፡፡

 

ሽኝቱ የተደረገላቸው ቀደም ሲል በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በምክትል ቢሮ ኃላፊነት ሲያገለግሉ ለነበሩት ለአቶ ሳመሶን መለሰ እና አቃቂ ቃሊቲ ክፍለከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ በመሆን ሲያገለግሉ ለቆዩት አቶ አለልኝ ወልዴ ሲሆን በሽኝት መርሀ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የማኔጅመንት እና የፕሮሰስ ካውንስል አባላትን ጨምሮ የክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በሽኝት ፕሮግራሙ ባስተላለፉት መልዕክት በዛሬው እለት የሚሸኙት አመራሮች በትምህርት ሴክተሩ በነበራቸው ቆይታ በሴክተሩ ለተመዘገበው ውጤት ያበረከቱት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው አሁን በተመደቡበት ዘርፍም ለትምህርት ሴከክተሩ የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ እምነታቸው መሆኑን በመግለጽ በተመደቡበት ሴክተር መልካም እድል እንዲገጥማቸውና በስራቸውም ውጤታማ እንዲሆኑ የመልካም ምኞት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

 

ሽኝቱ የተደረገላቸው አቶ ሳምሶን መለሰ እና አቶ አለልኝ ወልዴ በመርሀ ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት በአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ እና በክፍለከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤቶች ለተደረገላቸው የክብር ሽኝት ላቅ ያለ ምስጋና  በማቅረብ በትምህርት ሴክተሩ በነበራቸው ቆይታ ያካበቱት የስራ ልምድም ሆነ በጋራ የመስራት ባህል አሁን በተመደቡበት ሴክተር ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያግዛቸው መሆኑን አስረድተዋል፡፡

 

 

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

 

You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...

 

TikTok- tiktok.com/@aaeducationbureau

 

Telegram https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

 

Twitter https://twitter.com/aacaebc

 

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

 

Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/

 

Website: - aaceb.gov.et

 

Email;- aacaebc@gmail.com

 

Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/